ኢየሱስን እንዴት መከተል እንደሚቻል
Video not available
የአዲሱን ህይወትዎን 4 ዝምድናዎች የሚያብራራውን ይህን ጠቃሚ ቪዲዮ ይመልከቱ
ከታች ያሉት ክፍሎች፣ የኢየሱስ ተከታይ (ደቀ መዝሙር) መሆን ምን ማለት እንደሆነ ያስተምርዎታል
ይመዝገቡእግዚአብሔር ተራ ሰዎችን ተጠቅሞ ቀላል ነገሮችን በማድረግ እንዴት ትልቅ ተፅዕኖ እንደሚፈጠር የምትመለከቱ ይሆናል።
ደቀ መዝሙር የመሆን፣ ደቀ መዝሙር የማድረግን መሰረት እና ቤተ ክርስቲያን ማለት ምን እንደሆነ እወቁ።
አንድን ሰው የኢየሱስ ተከታይ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በመጪዎቹ ትውልዶች የሚበዛውን መላውን መንፈሳዊ ቤተሰብ ተከታይ የምታደርጉበትን ቀላል መንገድ ተማሩ።
እግዚአብሔር የዕለት ተዕለት ተከታዮችን ኢየሱስን እንዲመስሉ ለማድረግ የሚጠቀምባቸውን አራት ዋና መንገዶች ታውቃለችሁ።
ጸሎት
ደቀ መዝሙር መሆን ማለት እግዚአብሔርን እንሰማለን፣ ከዚያም እንታዘዘዋለን ማለት ነው።
አንድ ሰአት በጸሎት ማሳለፍ እንዴት ቀላል እንደሆነ ተመልከቱ።
ለሌሎች መጸለይ የምትችሉባቸውን መንገዶች የምታስታውሱበትን ቀላል የማስታወሻ ዘዴን ተለማመዱ።
የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ
የእግዚአብሔርን ቃል እንድትረዱ፣ እንድትታዘዙ ከዚያም እንድታካፍሉ የሚረዳችሁ የየዕለት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መገልገያ ነው።
ደቀ መዛሙርት የሚያውቁት ነገር መኖሩ አስፈላጊ ቢሆንም በሚያውቁት ነገር የሚያደርጉት ነገር ደግሞ ይበልጥ በጣም አስፈላጊ ነው።
ማህበረሰብ
የ3/3 ቡድን ማለት የኢየሱስ ተከታዮች የሚገናኙበት፣ የሚጸልዩበት፣ የሚማሩበት፣ በመንፈሳዊ ነገር የሚያድጉበት፣ የሚተባበሩበት ብሎም የተማሩትን በመታዘዝ የሚለማመዱበት መንገድ ነው። በዚህ መንገድ ስንመለከተው፣ የ3/3 ቡድን አነስተኛ ቡድን ብቻ ሳይሆን ቀላል ቤተክርስቲያን ጭምር ነው።
ሁለት ወይም ሶስት ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው ሰዎች በየሳምንቱ የሚገናኙበት እና በጥሩ ሁኔታ ላይ ባሉ አካባቢዎች እርስ በእርስ ለመበረታታት እና እርማት የሚያስፈልጋቸው ቦታዎችን የሚያሳዩ መገልገያዎች።
በመሄድና በመቆየት የኢየሱስን ትዕዛዛት እንዴት መታዘዝ እንደምትችሉ ተማሩ።
ይህም ከኢየሱስ ጋር ያለንን የቅርብ ግንኙነትና ጥልቀት ያለው ግንኙነት የምናከብርበት ቀላል መንገድ ነው። የምታከብሩበትን ቀለል ያለ መንገድ ተማሩ።
ኢየሱስ ‹‹ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤›› ብሎ የተናገረውን እንዴት ወደ ተግባር ማምጣት እንደምትችሉ ተማሩ።
መስዋዕትነትና መከራ
የእግዚአብሔር ኢኮኖሚ ከዓለም እንዴት እንደሚለይ ተማሩ። እግዚአብሔር ታማኝ ለሆኑት አስቀድሞ በተሰጣቸው ነገር ላይ የበለጠ ኢንቨስት ያደርጋል።
የእግዚአብሔር መንግሥት ያልደረሰነበትን ቦታ ማየት ጀምሩ። እነዚህ አብዛኛውን ጊዜ እግዚአብሔር በሙላት መስራት የሚፈልግባቸው ቦታዎች ናቸው።
ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱ ወዳሉበት ቀርቦ እንዲህም አላቸው፤ ‹‹ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጥቶኛል፤ ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ አስተምሯቸው፤ እኔም እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋራ ነኝ።››
ሌሎች ኢየሱስን እንዲታዘዙ እና ከእናንተ ጋር እንዲከተሉ ማስተማር
ትንሽ ዳክዬ ደቀ መዛሙርት ከማድረጉ ጋር ምን ግንኙነት እንዳላቸው እወቁ።
የስልጠና ዑደቱን ተማሩ እናም ደቀ መዛሙርት በማድረጉ ላይ እንዴት ተግባራዊ እንደሚሆን አስቡ።
ደቀ መዝሙር ማድረግ የግድ ቀጥተኛ መሆን እንደሌለበት ተመልከት። በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥ ብዙ ነገሮች ሊከሰቱ ይችላሉ።
ጉዳዮች ማብዛትና በፍጥነት ማብዛት ይበልጥ አስፈላጊ ነው። ፍጥነት ለምን አስፈላጊ እንደሆነ ተመልከቱ።
ለምታውቋቸው ሰዎች ስለ ኢየሱስ መናገር
የዝምድናዎቻችሁ ጥሩ ባለአደራ እንድትሆኑ ለማገዝ የተዘጋጀ መገልገያ።
የእግዚአብሔርን የምሥራች ዜና ከሰው ልጅ መጀመሪያ ጀምሮ እስከዚህ ዘመን ፍጻሜ ድረስ የማካፈል መንገድ ተማር።
ኢየሱስ እንዴት ህይወታችሁን እንደለወጠ በማካፈል ምስክርነታችን በሶስት ደቂቃ ውስጥ እንዴት ማካፈል እንደሚችሉ ተማሩ።
ለማታውቋቸው ሰዎች ስለ ኢየሱስ መናገር
የሰላም ሰው ማን ሊሆን እንደሚችል እና መቼ አግኝታችኋቸው እንደሆነ ማወቅ እንደምትችሉ እወቁ።
ለሌሎች እንድንጸልይ እግዚአብሔር ያዘዘንን ትዕዛዝ የምንታዘዝበት ቀላል መንገድ ነው። እና የሚገለጸውም ልክ በመመላለስ ላይ ሆኖ ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ ነው!
ይህ ቡድን የ3/3 ቡድኖችን እየመሩና እየጀመሩ ያሉ ሰዎችን ያቀፈ ነው። የ3/3 ቅርፀት የሚከተል ሲሆን በአካባቢያችሁ ያለውን የእግዚአብሔርን ስራ መንፈሳዊ ጤናማነት የምትገመግሙበት ብርቱ መንገድ ነው።
የሚበዙ ደቀ መዛሙርት ለማድረግ በሚቻልበት ጊዜ የራሳችሁን ጥንካሬ እና ተጋላጭነቶች በፍጥነት ለመገምገም መጠቀም የምትችሉበት ብርቱ መገልገያ ነው።
የአመራር ክፍሎች ለመምራት የተጠራ እንደሆነ የሚሰማው ሰው ማገልገልን በመለማመድ አመራሩን የሚያዳብርበት መንገድ ነው።
ብዙ አብያተ ክርስቲያናት ተገናኝተው በመቆየት እንዴት እንደ ትልቅ መንፈሳዊ ቤተሰብ አብረው እንደሚኖሩ እወቁ።