tool

ጥምቀት እና እንዴት ማጥመቅ እንደሚቻል

ይህን ገጽ ያጋሩ

ጥምቀት አዲሱን ሕይወታችንን የሚያሳይ ምስል ነው፤ በኢየሱስ አምሳል ተሰርጎ በእግዚአብሔር መታዘዝ የተለወጠ ሕይወት። ኢየሱስ ስለ ኃጢአታችን እንደ ሞተ ሁሉ፣ እኛም ለኃጢአት መሞታችንን የሚያሳይ ምስል ነው። ኢየሱስ እንደ ተቀበረ ሁሉ፣ የአሮጌ አኗኗራችን መቀበርን የሚያሳይ ምስል ነው። ኢየሱስ ከሙታን እንደ ተነሣ እና ዛሬም እንደሚኖር ሁሉ፣ በክርስቶስ ወደ አዲስ ሕይወት ዳግመኛ መወለዳችንን የሚያሳይ ምስል ነው። ኢየሱስም፣ ‹‹ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው...›› ብሏል። ጥምቀት ወይም በመጀመሪያው የግሪክ ቋንቋ Baptizo ማለት ሙሉ በሙሉ መንከር ወይም መስጠም ማለት ነው፤ ልክ ጨርቅ በቀለም ውስጥ ሲነከር ቀለሙን ሙሉ በሙሉ ወስዶ ተለውጦ እንደሚወጣ ነው።

አንድን ሰው እንዴት ማጥመቅ እንደሚቻል

ከዚህ በፊት አንድን ሰው አጥምቀው የማያውቁ ከሆነ፣ የሚያስፈራ ሊመስል ይችላል፤ ግን እንዲህ መሆን የለበትም። እነሆ with some simple steps:

  • አዲሱ ደቀ መዝሙር ሙሉ በሙሉ እንዲሰጥም የሚያስችል በቂ ጥልቀት ያለው የቆመ ውኃ ያግኙ። ይህ ኩሬ፣ ወንዝ፣ ሐይቅ ወይም ባሕር ሊሆን ይችላል። የመታጠቢያ ገንዳ ወይም ውኃ ለመሰብሰብ ሌላ መንገድም ሊሆን ይችላል።
  • ደቀ መዝሙሩ አንዱን እጃችሁን በእጁ እንዲይዝ አድርጉ፣ በሌላውም እጃችሁ ጀርባውን ደግፉ።
  • ውሳኔውን መረዳቱን ለማረጋገጥ እንደዚህ ያሉ ሁለት ጥያቄዎችን ጠይቁ። “ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ጌታህና አዳኝህ ተቀብለሃል?” “ከዚህ በኋላ በቀሪው ሕይወትህ ሁሉ እንደ ንጉሥህ ታዘዘው እና ታገለግለዋለህ?”
  • ለሁለቱም “አዎን” ብለው ከመለሱ፣ እንዲህ ያለ ነገር በሉ፤ “በጌታ ኢየሱስ ላይ እምነትህን ስለ መሰከርህ፣ አሁን በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቅሃለሁ።”
  • ወደ ውኃው እንዲወርድ እርዱት፣ ሙሉ በሙሉ አስሰጥሙት፣ ከዚያም እንደገና ከውኃው አውጡት።

እንኳን ደስ አላችሁ! አዲስ የኢየሱስ ተከታይ — አዲስ የሰማይ ዜጋ — አዲስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ አጥምቃችኋል። አሁን ለደስታ የምናከብርበት ጊዜ ነው!

እራሳችሁን ጠይቁ

  • ተጠምቀሃል? ካልሆነ፣ ስለዚህ ከአንድ አማኝ ጋር ተነጋግረህ ይህን ቀጣይ የመታዘዝ እርምጃ ከማን ጋር ልትወስድ ትችላለህ?
    • ከዚህ በፊት አንድን ሰው አጥምቀህ ታውቃለህ?
    • እንኳን ቢሆን ይህን ማድረግ ታስብበታለህ?
    • ታላቁ ተልዕኮ ለእያንዳንዱ የኢየሱስ ተከታይ ከሆነ፣ ሁሉም የኢየሱስ ተከታይ ሌሎችን እንዲያጠምቅ ተፈቅዶለታል ማለት ነውን? ለምን ወይም ለምንስ አይሆንም?

የZúme ስልጠናን ዛሬ ይጀምሩ

ሙሉ በሙሉ ነፃ ነው፣ እናም በማንኛውም ጊዜ መጀመር ይችላሉ—የትም ቢሆኑ በራስዎ ፍጥነት ይሂዱ።

በነጻ ይመዝገቡ