concept

መንግሥቱ የሌለበትን የሚመለከቱ አይኖች

ይህን ገጽ ያጋሩ

እያንዳንዱ ደቀ መዝሙር መንግሥቱ የሌለበትን ቦታ ማየት እንዲችል መታጠቅ ያስፈልገዋል። በዙሪያችን ሁሉ በምድር ላይ እንደ ሰማይ የእግዚአብሔር ፈቃድ ያልተፈጸመባቸው ቦታዎች አሉ። ስብራት፣ ሕመም፣ ስደት፣ መከራ እና እንኳን ሞት የመደበኛ የዕለት ተዕለት ሕይወት አካል የሆኑባቸው ትልልቅ ክፍተቶች አሉ። እነዚህን ክፍተቶች እኛ በምድር ላይ እስካለን ድረስ ለመንግሥቱ በምናደርገው ሥራ ለመዝጋት ልንሠራባቸው ይገባል።

መንግሥቱ የሌለበትን ቦታ ለማየት ዓይኖቻችንን መክፈት እና በምናውቃቸው ሰዎችም ሆነ ገና ባላገኘናቸው ሰዎች ዘንድ መድረስ ደቀ መዛሙርት የሚበዙበትና የእግዚአብሔር መንግሥት ሩቅና ፈጣን የሚያድግበት መንገድ ነው።

በምድር ላይ የእግዚአብሔር ፈቃድ ፍጹም በሆነ ሁኔታ ከሚፈጸምበት እና አሁን ካለው ሁኔታ መካከል ያሉትን ክፍተቶች ማየት ያስፈልገናል። ይህም በሁለት መስኮች ሊሆን ይገባል፦

ቀጣይ ግንኙነቶች

የመጀመሪያው መስክ ቀጣይ ግንኙነቶቻችን ነው። ይህም ጓደኞቻችንን፣ ቤተሰቦቻችንን፣ የሥራ ባልደረቦቻችንን፣ አብረውን የሚማሩ ተማሪዎችን እና ምናልባትም ጎረቤቶቻችንን ያካትታል። ወንጌል በጣም ፈጣን የሚጓዝበት መንገድ ይህ ነው። ለእነዚህ ሰዎች መጨነቅ ተፈጥሯዊ ነው። በሉቃስ 16፥19-31 እንደምናየው በሲኦል ውስጥ የሚነድው ባለጠጋ እንኳን ለቤተሰቡ ይህን ዓይነት ፍቅርና አሳቢነት ነበረው። እነዚህን ሰዎች እግዚአብሔር በሕይወታችን ውስጥ አኑሯቸዋል፣ እኛም እነዚህን ግንኙነቶች በፍቅር፣ በትዕግሥት እና በጽናት በሚገባ ልንይዛቸው ይገባል።

የ100 ዝርዝር እንዲጽፉ በማድረግ የክርስቶስን ተከታዮች ለዚህ የሰዎች ቡድን ንቁ ማድረግ ትችላላችሁ። እነርሱንም በሦስት ምድቦች እንዲከፍሏቸው አበረታቷቸው፦ ክርስቶስን የሚከተሉ፣ ክርስቶስን የማይከተሉ፣ እና መንፈሳዊ ሁኔታቸው የማይታወቅ ሰዎች።

ከዚያም ክርስቶስን የሚከተሉት የበለጠ ፍሬያማና ታማኝ እንዲሆኑ ለማስታጠቅና ለማበረታታት መፈለግ ይችላሉ። እስካሁን ክርስቶስን የማይከተሉትንም ወደ መንግሥቱ ለመምራት “ደቀ መዛሙርት ለማድረግ” መንገዶችን መፈለግ ሊጀምሩ ይችላሉ።

ከቀጣይ ግንኙነቶቻችን ውጭ ያሉ ግንኙነቶች እና ሰዎች

ሁለተኛው መስክ መንግሥቱ የሌለበትን ቦታ ማየት ከቀጣይ ግንኙነቶቻችን ወይም ከምናውቃቸው ሰዎች ውጭ ካሉት ጋር ይዛመዳል። ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ በምድር ላይ ካሉ ሕዝቦች ሁሉ ደቀ መዛሙርት እንዲያደርጉ አዘዛቸው።

እነርሱ ባሉበት ቦታ እንዲሁም በአቅራቢያ ባሉ ስፍራዎች፣ ከራሳቸው የተለዩ ሰዎች መካከል፣ እንዲያውም እስከ “ምድር ዳርቻ” ድረስ ደቀ መዛሙርት እንዲያደርጉ አዘዛቸው። ወንጌል እጅግ ሩቅ የሚጓዝበት መንገድ ይህ ነው። ይህ ተፈጥሯዊ አይደለም። ይህ በላይኛው ኃይል የሚሆን ነው። ይህም በሕይወታችን ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ መገኘት ምልክት ነው።

እግዚአብሔር የሚበልጥ የሚጨነቅላቸው ሰዎች አሉት። እነርሱም ከሁሉ ያነሱት፣ ወደ ኋላ የቀሩት እና የጠፉት ናቸው። ስለዚህ ሕይወታችንን ለማገልገል የምናፈስሰው በቅርባችን ላሉት ብቻ ሳይሆን በዓለም ላይ በጣም በመንፈሳዊ ጨለማ ውስጥ ላሉትም ማገልገል ላይ መሆን አለበት። እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል። እኛም እጅግ የተጨነቁ ሰዎችን ልናገለግል ይገባል። እጅግ የተጨነቁ ሰዎች ብዙ ጊዜ ከሁሉ የበለጠ ትሑታን ይሆናሉ። ከእነዚህ አይነት ሰዎች መካከል በተለይ ታማኝ የሆኑትን ፈልገን በእነርሱ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ያስፈልገናል።

ታማኝነት የሚታየው እግዚአብሔር ለሚገልጠው ነገር በመታዘዝ እና ያንንም ለሌሎች በማካፈል መሆኑን አስታውሱ። እነዚህ ሰዎች በኢየሱስ ምሳሌ ውስጥ እንዳለው መልካም መሬት ናቸው። ሠላሳ፣ ስድሳ ወይም መቶ እጥፍ ፍሬ የሚያፈሩ እነርሱ ናቸው። መልእክቱን የሚጥሉ ጠንካራ ልብ ያላቸው አይደሉም። ስደት ሲመጣ ወዲያው የሚወድቁ አይደሉም። በዓለም ጭንቀት ወይም በባለጠግነት ምቾት የሚዘናጉ አይደሉም። እነርሱ ኢየሱስ ስላደረገለት ነገር በመታዘዝና ለሌሎች በማካፈል ለኢየሱስ አገልግሎት ምላሽ እንደሰጠው እንደ ጌራሴናዊው አጋንንት የያዘው ሰው ናቸው። በዚህም ምክንያት ኢየሱስ በኋላ ወደዚያ ክልል በተመለሰ ጊዜ ብዙ ሰዎች እርሱን ይፈልጉ ነበር።

እራሳችሁን ጠይቁ

  • ለማካፈል የበለጠ የሚመችህ ከማን ጋር ነው -- አስቀድመህ ከምታውቃቸው ሰዎች ወይስ ገና ካላገኘኃቸው ሰዎች ጋር?
    • ይህ እንደዚህ የሆነ ለምን ይመስልሃል?
    • ከማትመችባቸው ሰዎች ጋር በተሻለ ሁኔታ ለማካፈል እንዴት ልትሻሻል ትችላለህ?

የZúme ስልጠናን ዛሬ ይጀምሩ

ሙሉ በሙሉ ነፃ ነው፣ እናም በማንኛውም ጊዜ መጀመር ይችላሉ—የትም ቢሆኑ በራስዎ ፍጥነት ይሂዱ።

በነጻ ይመዝገቡ