የጌታ እራት እና እንዴት አንዲከናወን ማድረግ እንደሚቻል
ጌታ ኢየሱስ እንዲህ አለ፦ ‹‹እግዚአብሔር ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ማንም ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ ይህም እንጀራ፣ ለዓለም ሕይወት እንዲሆን የምሰጠው ሥጋዬ ነው።›› ቅዱስ ቁርባን ወይም “የጌታ እራት” ከኢየሱስ ጋር ያለንን የቅርብ ግንኙነትና ቀጣይነት ያለውን ህብረት የምናከብርበት መንገድ ነው። እነሆ፣ የምታከብሩበት ቀላል መንገድ!
እንደ ኢየሱስ ተከታዮች በምትሰበሰቡበት ጊዜ፣ በጸጥታ ቆዩና ስለ ኃጢአታችሁ በልባችሁ አስቡ እና ተናዘዙ። ዝግጁ ስትሆኑ፣ አንድ ሰው ይህን ክፍል ከቅዱሳት መጻሕፍት ያንብብ -- ‹‹እኔ ደግሞ ለእናንተ አሳልፌ የሰጠሁትን ከጌታ ተቀብያለሁና፤ ጌታ ኢየሱስ አሳልፈው በሰጡት ሌሊት እንጀራን ወሰደ፤ አመስግኖም ቆረሰና፦ “ይህ ስለ እናንተ የሚሰጥ ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለማስታወስ አድርጉት” አለ።›› 1 ቆሮንቶስ 11:23-24
ለቡድናችሁ ያዘጋጃችሁትን እንጀራ አካፍሉ እና ብሉ።
ንባቡን ቀጥሉ -- ‹‹እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ወስዶ፦ “ይህች ጽዋ በደሜ ያለች አዲስ ኪዳን ናት፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለማስታወስ አድርጉት” አለ።›› 1 ቆሮንቶስ 11:25
ለቡድናችሁ ያዘጋጃችሁትን ጭማቂ ወይም ወይን አካፍሉ እና ጠጡ።
ንባቡን በዚህ ጨርሱ፦ ‹‹ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ሁሉ ጽዋውንም በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ታውጃላችሁና።›› 1 ቆሮንቶስ 11:26
በጸሎት ወይም በመዝሙር አክብሩ። በየጌታ እራት ተካፍላችኋል። እናንተ የእርሱ ናችሁ፣ እርሱም የእናንተ ነው!
እራሳችሁን ጠይቁ
- መጽሐፍ ቅዱስ ቁርባንን ለመካፈል የሚያስፈልገው እና የማያስፈልገው ምን እንደሆነ ምን ይላል?
የZúme ስልጠናን ዛሬ ይጀምሩ
ሙሉ በሙሉ ነፃ ነው፣ እናም በማንኛውም ጊዜ መጀመር ይችላሉ—የትም ቢሆኑ በራስዎ ፍጥነት ይሂዱ።
በነጻ ይመዝገቡ