እንዴት አንድ ሰዓት በጸሎት ውስጥ ማሳለፍ እንደሚቻል
የጸሎት ዑደት በእራስዎ ሊጠቀሙበት እና ለማንኛውም የኢየሱስ ተከታይ ሊያካፍሉት የሚችሉት ለጸሎት ልምምድ የሚረዳ ቀላል መሳሪያ ነው። በ12 ቀላል ደረጃዎች - እያንዳንዳቸው 5 ደቂቃ - የጸሎት ዑደት መጽሐፍ ቅዱስ እንድንጸልይ የሚያስተምረንን 12 መንገዶች ያሳያችኋል። በመጨረሻ ላይ አንድ ሰዓት ጸልያችሁ ትሆናላችሁ። መጽሐፍ ቅዱስም -- “ሳታቋርጡ ጸልዩ።” ይለናል። ብዙዎቻችን ይህን እናደርጋለን ማለት አንችልም። ነገር ግን ከዚህ የአንድ ሰዓት ጸሎት በኋላ - አንድ እርምጃ ወደዚያ ቀርባችኋል።
በ12 ቀላል ደረጃዎች - እያንዳንዳቸው 5 ደቂቃ - ይህ የጸሎት ዑደት መጽሐፍ ቅዱስ እንድንጸልይ የሚያስተምረንን 12 መንገዶች ውስጥ ይመራችኋል። በመጨረሻ ላይ አንድ ሰዓት ጸልያችሁ ትሆናላችሁ።
**አመስግኑ** - የጸሎት ሰዓታችሁን ጌታን በማመስገን ጀምሩ። አሁን በልባችሁ ላይ ስላሉ ነገሮች አመስግኑት። ባለፈው ሳምንት በሕይወታችሁ ውስጥ ስላደረገው አንድ ልዩ ነገር አመስግኑት። ለቤተሰባችሁ ስላደረገው ቸርነት አመስግኑት።
**ጠብቁ** - ጌታን በመጠበቅ ጊዜ አሳልፉ። ዝም በሉ እና ለእናንተ የሚሆኑ ሐሳቦችን እንዲሰበስብላችሁ ፍቀዱለት።
**ኑዛዜ ግቡ** - መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችሁ ውስጥ እርሱን ደስ የማያሰኝ ማንኛውንም ነገር እንዲያሳያችሁ ጠይቁት። የተሳሳቱ አመለካከቶችን እንዲሁም እስካሁን ኑዛዜ ያልገባችሁባቸውን የተወሰኑ ተግባራት እንዲያሳያችሁ ጠይቁት። አሁንም እንድትነጹ ይህን ለጌታ ተናዘዙ።
**ቃሉን አንብቡ** - በመዝሙር መጽሐፍ፣ በነቢያት መጻሕፍት ወይም በአዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ ጸሎት የሚናገሩ ክፍሎችን በማንበብ ጊዜ አሳልፉ።
**ለምኑ** - ስለ እራሳችሁ የሚሆኑ ልመናዎችን አቅርቡ።
**ምልጃ** - ስለ ሌሎች የሚሆኑ ልመናዎችን አቅርቡ።
**ቃሉን ጸልዩ** - የተወሰኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን ጸልዩ። በተለይም የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሎቶች እና ብዙ መዝሙሮች ለዚህ ዓላማ በጣም ይረዳሉ።
**አመስግኑ** - በሕይወታችሁ ውስጥ ስላሉ ነገሮች፣ ስለ ቤተሰባችሁ እና ስለ ቤተ ክርስቲያናችሁ ጌታን አመስግኑት።
**ዘምሩ** - የምስጋና ወይም የአምልኮ መዝሙሮችን ወይም ሌላ መንፈሳዊ መዝሙር ዘምሩ።
**አሰላስሉ** - ጌታ እንዲናገራችሁ ጠይቁት። የሚሰጣችሁን ሐሳብ ለመመዝገብ ብዕርና ወረቀት ዝግጁ አድርጉ።
**አድምጡ** - ያነበባችሁትን፣ የጸለያችሁትን እና የዘመራችሁትን ነገር አንድ ላይ በማድረግ ጌታ እነዚህን ሁሉ እንዴት በአንድ ላይ አድርጎ እንደሚናገራችሁ ተመልከቱ።
**አመስግኑ** - ከእርሱ ጋር ለቆያችሁት ጊዜ እና ስለሰጣችሁ ሐሳቦች ጌታን አመስግኑት። ስለ ክቡር ባሕርያቱ አመስግኑት።
ከዲክ ኢስትማን The Hour that Changes the World © 2002 by Dick Eastman, Chosen Books, Grand Rapids, MI, used by permission.
**አመስግኑ** - የጸሎት ሰዓታችሁን ጌታን በማመስገን ጀምሩ። አሁን በልባችሁ ላይ ስላሉ ነገሮች አመስግኑት። ባለፈው ሳምንት በሕይወታችሁ ውስጥ ስላደረገው አንድ ልዩ ነገር አመስግኑት። ለቤተሰባችሁ ስላደረገው ቸርነት አመስግኑት።
**ጠብቁ** - ጌታን በመጠበቅ ጊዜ አሳልፉ። ዝም በሉ እና ለእናንተ የሚሆኑ ሐሳቦችን እንዲሰበስብላችሁ ፍቀዱለት።
**ኑዛዜ ግቡ** - መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችሁ ውስጥ እርሱን ደስ የማያሰኝ ማንኛውንም ነገር እንዲያሳያችሁ ጠይቁት። የተሳሳቱ አመለካከቶችን እንዲሁም እስካሁን ኑዛዜ ያልገባችሁባቸውን የተወሰኑ ተግባራት እንዲያሳያችሁ ጠይቁት። አሁንም እንድትነጹ ይህን ለጌታ ተናዘዙ።
**ቃሉን አንብቡ** - በመዝሙር መጽሐፍ፣ በነቢያት መጻሕፍት ወይም በአዲስ ኪዳን ውስጥ ስለ ጸሎት የሚናገሩ ክፍሎችን በማንበብ ጊዜ አሳልፉ።
**ለምኑ** - ስለ እራሳችሁ የሚሆኑ ልመናዎችን አቅርቡ።
**ምልጃ** - ስለ ሌሎች የሚሆኑ ልመናዎችን አቅርቡ።
**ቃሉን ጸልዩ** - የተወሰኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን ጸልዩ። በተለይም የመጽሐፍ ቅዱስ ጸሎቶች እና ብዙ መዝሙሮች ለዚህ ዓላማ በጣም ይረዳሉ።
**አመስግኑ** - በሕይወታችሁ ውስጥ ስላሉ ነገሮች፣ ስለ ቤተሰባችሁ እና ስለ ቤተ ክርስቲያናችሁ ጌታን አመስግኑት።
**ዘምሩ** - የምስጋና ወይም የአምልኮ መዝሙሮችን ወይም ሌላ መንፈሳዊ መዝሙር ዘምሩ።
**አሰላስሉ** - ጌታ እንዲናገራችሁ ጠይቁት። የሚሰጣችሁን ሐሳብ ለመመዝገብ ብዕርና ወረቀት ዝግጁ አድርጉ።
**አድምጡ** - ያነበባችሁትን፣ የጸለያችሁትን እና የዘመራችሁትን ነገር አንድ ላይ በማድረግ ጌታ እነዚህን ሁሉ እንዴት በአንድ ላይ አድርጎ እንደሚናገራችሁ ተመልከቱ።
**አመስግኑ** - ከእርሱ ጋር ለቆያችሁት ጊዜ እና ስለሰጣችሁ ሐሳቦች ጌታን አመስግኑት። ስለ ክቡር ባሕርያቱ አመስግኑት።
ከዲክ ኢስትማን The Hour that Changes the World © 2002 by Dick Eastman, Chosen Books, Grand Rapids, MI, used by permission.እራሳችሁን ጠይቁ
- የጸሎት ሕይወታችሁን ለማሳደግ ምንን እንደገና ማስተካከል ወይም ማቆም ይኖርባችኋል?
የZúme ስልጠናን ዛሬ ይጀምሩ
ሙሉ በሙሉ ነፃ ነው፣ እናም በማንኛውም ጊዜ መጀመር ይችላሉ—የትም ቢሆኑ በራስዎ ፍጥነት ይሂዱ።
በነጻ ይመዝገቡ